ኢትዮ-ቴሌኮም ከዘርፉ ልኬቶች አንፃር

ኢቲዮ-ቴሌኮም እስካሁን ድረስ ስለ ስኬቱ የሚነግረን፤ ህብረተሰቡም ሲያደንቀው የሚስተዋለው በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ገቢ ማግኘቱን በመግለፅ ነው።

በአንፃሩ፣ ጠ/ሚ አብይ ባንድ ወቅት “ቴሌ ውጤታማ ሆነ የሚባለው የዜጎችን ኑሮ፣ የገበሬውን ምርታማነት፣ ግብይቱን፣ የመንግስትን አገልግሎት አሰጣጦችን፣ የዲጂታል የስራ እድል ወዘተ.. አውቶሜት አድርጎ ኑሮን ማሻሻልና የዜጎችን ስኬት ማቃለል ከቻለ ብቻ ነው” ማለታቸውን ልብ በሉ።
ልክ ነው። ኢቲዮ-ቴሌኮም በሞኖፖሊ በያዘው አገልግሎት 120 ሚሊዮን ዜጋ በሚኖርባት ሀገር ተጠቃሚውም አማራጭ ሳይኖረው አንድ ለናቱ ከሆነው ኩባንያ ደንበኛ በሆነባት ሀገር ላይ፣ ትርፍ እና የደምበኛ ቁጥር እንደ ስኬት በዬአመቱ ማቅረብ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ ነው።

ጠቅላይ ምኒስትሩ በጠቀሱት የዘርፉ መለኪያ ኢትዮ ቴሌኮም ከአለም የያዘው ደረጃ ወደ መጨረሻ ላይ ነው የሚገኘው። ከስድስት ያልበለጡ ሀገራትን ነው የምንበልጠው። “ግሎባል ሬዲነስ ኢንዴክስ” ከ 120 ሀገራት አንፃር 2019 ላይ ያወጣውን ሪፖርት እንመልከት። የኢትዮ ቴሌኮም ደረጃ የሚከተለው ነው።

 ▪️መለኪያ                               ▪️ነጥብ    ▪️ደረጃ
  1. በኢንተኔት ግብይት… …………….. 0 115
  2. ከዘመኑ ዲጅታል አሰራር መጣጣም.. 31 94
  3. የዜጎች ዲጂታል ተሳትፎ ………. 51 91
  4. የዜጎችን ሶሺዮ ኢኮኖሚያዊ gap … 19 115
  5. ዌብሳይት ያላቸው ድርጅቶች ….. 21 92
  6. ዲጂታል ክፍያ ………….. 50 95
  7. የኢንተርኔት ተጠቃሚ ከማድረግ …. – – 113
    9, የሞባይል ብሮድባንድ ተጠቃሚ…. 4.86 115
  8. (ሀገራዊ ይዘት በኢንተርኔት፣
    Local content፡
    eg; የቢዝነስ-ቱሪዝም መስኮችን
    ለአለም ተደራሽ ማድረግ ——– 24 102
  9. Use of virtual social networks 2.9 111
  10. E-commerce legislation…….. 50 100
  11. ICT regulatory
    environment……. 20 119
  12. Secured internet service ………….. o 115

በአጠቃላይም እነ የመንን የመሳሰሉ ሀገራትን ስንበልጥ ሶማሊያን አይነቶቹ በብዙ መለኪያ ወደ ላይ ተቀምጠው ይገኛሉ።

Source , Global readiness Index – 2019 👇

https://www.google.com/url?sa=t&source=web&rct=j&url=https://www.cisco.com/c/m/en_us/about/corporate-social-responsibility/research-resources/digital-readiness-index.html&ved=2ahUKEwiM0_DkmOz6AhVPXvEDHRLWCH8QFnoECAkQAQ&usg=AOvVaw1r7F8sqcJJfWtAtoPNcOED

Share:

Share on facebook
Share on twitter
Share on linkedin
Share on pinterest

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

On Key

Related Posts

VK Russian online social media and social networking service

© 2022 Esleman Abay. All rights reserved.

Follow Us

Categories