እንግሊዝ በኢትዮጵያ ግድብ መገንባት ያቀደችበት ታሪክ

The Nile

ግብፅ ውስጥ ለሚገኘው አስዋን ግድብ ውሀ የሚያቀርብ ሌላ ግድብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊሰራ ታቅዶ ነበር

በአሜሪካን ሀገር መኖርያቸውን ያደረጉት የምህንድስና ባለሙያው እና በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ጥናቶችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማሳወቅ የሚታወቁት አቶ ሲሳይ አለማየሁ ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር ባደረጉት ቆይታ ነው መረጃውን የተናገሩት።

እንግሊዝ ግብፅ ውስጥ በስፋት ጥጥ ታመርት ነበር፤ ያ ጥጥ ወደ እንግሊዝ ሄዶ የሱፍ ጨርቅ ይመረትበት ስለነበር፤ የአባይ ውሀ ፍሰት እንዳይቀንስ ትሰጋ ነበር፡፡ በግብጽ እና በሱዳን ለከፈቷቸው ኢንዱሰትሪዎች ቋሚ የጥጥ አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግም ቋሚ የውሀ አቅርቦት ያስፈልግ ነበር፡፡ አስዋን ግድብ እንደተገነባ፤ እድሜው እንዲረዝምና በቋሚነት ውሀ እንዲያቀርብ እንግሊዞች ኢትዮጵያ ውስጥ ግድብ እንዲገነባ አቋም ይዘው ነበር፡፡ አንደኛ እንደ ድርቅ ያለ የችግር ጊዜ ሲመጣ መጠባበቂያ ግድብ ውሀ እንዲለቅ ነበር የታሰበው፡፡
ሀይለኛ ጎርፍ ቢመጣም፣ እየበረደ ሱዳንን አልፎ ወደ ግብፅ ይደርሳል ተብሎ ታስቦ እንደነበር ነግረውናል፡፡
ሌላው እንግሊዞች በወቅቱ አስበውት የነበረው፤ በትነት ውሀ እንዳያጡ ይሰጉ ስለነበር፤ ከጣና ሀይቅ በመጥለፍ በቱቦ አድርጎ ውሀውን መውሰድ ነበር፡፡

ታዲያ የህዳሴ ግድቡ ለግብፅ ያለውን ጠቀሜታ እንግሊዝም ቀድማ ያስገነዘበቻት ሀቅ ሆኖ እያለ ቅዠትን መንገዷ አድርጋለች።

Share:

Share on facebook
Share on twitter
Share on linkedin
Share on pinterest

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

On Key

Related Posts

VK Russian online social media and social networking service

© 2022 Esleman Abay. All rights reserved.

Follow Us

Categories