የአናቶሊያ ፕሮጀክት GAP በኤፍራጥስ-ጢግሪስ ተፋሰስና በላይኛው ሜሶፖታሚያ ሜዳማ ቦታዎች የሚገኙ 9 ግዛቶችን ይሸፍናል፡፡ ያካባቢያቸውን የውሃና መሬት ሀብት በመጠቀም የተገነባው ፕሮጀክቱ 10 በመቶ ቱርካዊያንን ገቢ እና የኑሮ ጥራት ማሻሻል አስችሏል፡፡
GAP 22 ግድቦችን፤ 19 የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎችን፤ በኤፍራጠስና ጢግረስ ተፋሰስ ውስጥ 1.8 ሚሊዮን ሄክታር መሬት የሚሸፍን የመስኖ አውታሮችን ያካትታል፡፡ የ አታቱርክ ግድብም በኢፍራጠስ ጢግረስ ወንዝ ተገንብተው በስራ ላይ ካሉት 5 ግድቦች ትልቁ በአሁኑ ጊዜ በኤፍራጥስ ወንዝ ላይ ከሚሰሩት አምስት ግድቦች ትልቁ ነው፡፡
በቱርክ የሚገኙ አፍሪካዊ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ለተሞክሮ ልውውጥ በ 2018 ላይ ፕሮጄክቱን ጎብኝተውታል። ተሳታፊ አምባሳደርና ዲፕሎማቶቻችን ዕውነታውን ለአገራችን ዲፕሎማሲ ማዋልም ይጠበቅባቸዋል።