
የዓባይ፡ልጅ እስሌማን፡ዓባይ
ኢትዮጵያውያኑ ስለ ሀገራቸው ጉዳይ የሚያሰሙት ድምፅ አሁንም ቀጥሏል። በውጭ እና በሀገር ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም ኤርትራዊያን እና የኢትዮጵያ ወዳጅ ዜጎች በተለይም ህወሃት ድጋሚ የከፈተውን ጦርነት በማውገዝ ረገድ ተሳትፏቸው በማደግ ላይ ይገኛል።
ትዊተር ላይ ከተሰራጩ መልእክቶች መካከል #TPLFisTheCause በሚለው ሀሽታግ ባለፉት ሰባት ቀናት ከ 312,000 በላይ መልእክቶችን አሰራጭተዋል። ይህ የዳታ አናሊቲክስ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ ባሉት 24 ሰአታት ብቻ መቶ ሺህ ያህል(97 ሺህ) መልእክቶች በተጠቀሰው ሐሽታግ ሊሰራጭ ችሏል።

በመላው አለም በሁሉም አህጉራትና ሀገሮች መዳረስ የጀመረው ይህ የህወሃትን ጦርነት የሚያወግዘው ሐሽታግ በሰሜን አሜሪካ ካናዳ አውሮፓ እስያ አውስትራሊያ ደቡብ አሜሪካ እንዲሁም አፍሪካ ሀገራት በሚኖሩ ዜጎች ያስተላለፉት መሆኑን የአናሊቲክስ ውጤቶቹ አመላክተዋል።
ከኢትዮጵያ የተሰራጩ መልእክቶች ብልጫ የወሰዱበት ከተጠቀሰው ሐሽታግ ጋር የተስተጋቡ ድምፆች ከኢትዮጵያ በመቀጠል በአሜሪካ፣ ኔዘርላንድ ህንድ ማሌዢያ ካናዳ ጣልያን እንግሊዝ ጀርመን የሚገኙ ትዊተር ተጠቃሚዎች የደረጃ ቅደም ተከተሉን ይዘው ይገኛል።

ህወሃት ድጋሚ ከከፈተው ጦርነት አስቀድሞ በህወሃት ደጋፊያን Tigray Under Attack በሚል ሐሽታግ የትዊተር ዘመቻዎች ሲደረጉ ይገኛሉ።

ከቀናት በፊት የተሰራው አናሊቲክስ የታየው ውጤት የኢትዮጵያኑን ድምፅ በብዙ እጥፍ መብለጡን ነበር። ህወሃትን የሚያወግዘው ሀሽታግ ስርጭትም በቀን ከአስር ሺህ ያልበለጠ ነበር።

አሁን ላይ ማንሰራራት ያሳየው የኢትዮጵያዊያን የትዊተር ዘመቻ የተመዘገበው ከ300 ሺህ በላይ ሳምንታዊ እና መቶ ሺህ የደረሰው ዕለታዊ ውጤት እየሞቀና እያደገ እንደሚቀጥል የሚጠበቅ ነው።
✍️ Esleman Abay
#የዓባይልጅ #eslemanabay