Ras alula abanega ራስ አሉላ አባነጋ

የዓባይ:ልጅ ✍️ እስሌማን ዓባይ ➖ Twitter: Esleman abay Facebook: Esleman Abay

የትግራዋይ ኢትዮጵያዊ ጀግንነት ሚዛን፣ የአንድነታችን ማገር፤ ዘመኑን ሙሉ ለኢትዮጵያ ክብር ሲዋደቅ የኖረ፤ ዕንደ ዕንቁ የከበረ የኢትዮጵያ ልጅ፣ ባለውለታችን– “..ዶጋሊ ላይ ዶጋመድ አረጋቸው..” በሚል ገለፃ የታሪክ መምህራችን ጋሽ አዛዥ [ዳሞት ት/ቤት፣ ፍኖተ ሰላም] ያስተማሩን አይረሳኝም፤ ለጓደኞቼም አይረሴ ነው..።

ዳሞት መሰናዶ ትምህርት ቤት፣ ፍኖተ ሰላም፣ ም/ጎጃም damot preparator school finote selam
ፍኖተ ሰላም Finote selam Town, capital-west gojjam administration

በፈረንጆቹ 1887፣ በቶማስ ዲ. ክርስቶፎር የተመራውን የኢጣሊያን 500 እግረኛ ጦር ለመፋለም 7000 የኢትዮጵያ እግረኛ ጦርን እየመሩ ወደ ዶጋሊ አውደ ውጊያ ዘመቱ – ራስ አሉላ እንግዳ (አሉላ አባነጋ)— ድንበራችንን ጥሰው የገቡ የጣሊያን ወራሪዎችን #ዶጋሊላይዶግአመድአደረጋቸው ~ ጣሊያን ያዘመተቻቸው 500 ወታደሮችን ደመሰሱ ~ 420ዎቹ የጣሊያን ወታደሮች ሲገደሉ የቀሩት 80ዎቹ ቆስለው ተማረኩ።

ጣሊያን░ሰሐጢ░ላይ░እግሩን░ቢዘረጋ፣
አንገብግቦ░ቆላው░አሉላ░አባነጋ፡፡ 

The Battle Field of Gura
from page 519 of Moslem Egypt and Christian Abyssinia; or, military service under the Khedive, by DYE, William MacE. British Library.

ይህ ሽንፈት ከፍተኛ ሕዝባዊ ቁጣ የቀሰቀሰባት ጣልያን በውጊያው ለተገደሉት ወታደሮቿ ሮም በሚገኝ Piazza dei Cinquecento በተባለ አደባባይ የመታሰቢያ ሐውልት ለማቆም ተገዳለች፡፡
ኢጣሊያ ሮም ላይ ካቆመችው ሃውልት በተጨማሪ ዶጋሊ በተባለውና ዛሬ ኤርትራ ውስጥ በሚገኘው ስፍራ ላይም ለሞቱት ወታደሮቿ ሌላ ሃውልት ገንብታ ነበር፡፡

The Gundet battle map

ያ’ሉላ░ፈረስ░የረገጣቸው፣ እስካሁን░ድረስ░አለ░ቁስላቸዉ።
የአሉላ░ፈረስ░ተስቦ░ወርዶ፣
ያንን░ነጭ░ገብስ░አረገዉ░ነዶ።

የዶጋሊ ድል የአሉላ አባ ነጋን ዝና ከጣሊያን ባሻገር መላው አውሮፓ በፍርሃት እንዲርድ ያደረገ ነበር። የኢትዮጲያን ስም በዓለም ዙሪያ በጀግንነት እንዲነሳ ያደረገ ሲሆን ለአድዋው ጦርነት መነሻም የመጀመሪያ ምዕራፍ መሆኑ ይገለፃል።

The battle of gura

አሉላ░አባነጋ░ካስመራ░ቢነሳ፣ ቢቸግረው░ጣሊያን░አለ░ፎርሳ░ፎርሳ።

አፄ ዮሐንስ በውስጥ ፖለቲካዊ ስራ ላይ በነበሩበት ጊዜ ቱርኮች ምፅዋን መያዛቸውን ሰሙ፤ ለራስ አሉላም እንዲህ ሲሉ ላኩባቸው፤ “እኔ እስክመጣ ድረስ ተጨማሪ ቦታ እንዳይዙ ነቅታችሁ ተጠባበቁ” የሚል..፡፡

ዮሐንስ░መብቱን░ላሉላ░ቢሰጠው፣
እንደቀትር░እሳት░ቱርክን░ገላመጠው፣
ጣልያንም░ወደቀ░እያንቀጠቀጠው፣
አጭዶና░ከምሮ░እንደገብስ░አሰጣው፡፡

“..መጥቼ እስክንዋጋቸው ድረስ በንቃት ጠብቁ..” የሚለው የአፄ ዮሐንስ መመሪያ የደረሳቸው ራስ አሉላ “ለጌታ ድግስ እንጂ ጦር አያቆዩትም!” በማለት ራሳቸው የሚመሩትን ጦር መርተው ትልቅ ጦርነት አደረጉና ድል አደረጉ፡፡

አሉላ░አባነጋ░የደጋ░ላይ░ኮሶ፣ በጥላው░ያደክማል░እንኳንስ░ተቀምሶ፡፡

Alula AbaNega አሉላ አባ ነጋ

ጀግናው አሉላ ከወራሪ ጋር ያደረጓቸውን ስምንት አውደ ውጊያዎች በድል ደምድመዋል:
⏹|ዘመናቱ ፈረንጅኛ ናቸው⤵️

▪️ጉንደት – ግብፅ+ኦቶማን – 1875
▪️ጉራዕ – ኦቶማን+ግብፅ – 1876
▪️አይለት- 1887
▪️ሰሃጢ -1880
▪️ኩፊት – መሀዲስት/ሱዳን – 1885
▪️ጋላባት /መተማ – 1889
▪️ሰሀጢ – ጣሊያን – 1887
▪️ዶጋሊ – 1887
▪️ዐምባላጄ – 1889
▪️መቐለ እና ዓድዋ – 1896

ራስ አሉላ አባ ነጋ በአፄ ዮሐንስ ዘመን ሐማሴንንና አካባቢውን ለረጅም አመታት አስተዳድረዋል፡፡
የመሃንዲስቶችን፣ የግብፆችን፣ የጣሊያኖችና የኦቶማኖችን ተደጋጋሚ የወረራ ጦርነት ድል ያደረጉት ጀግናው ራስ አሉላ ከንጉሠ-ነገስቱና ከመላው ህዝብ ትልቅ ከበሬታና ተደናቂነትን ሲያስገኝላቸው፤ ሀገሩ ኢትዮጵያን ጀግንነትም በአለም ዙሪያ በተለይም በምድረ አውሮፓ እንዲታወቅ ያደረጉ ባለውለታችን ናቸው፡፡

Alula Abanega international Airport mekelle አሉላ አባነጋ ዓለም ዓቀፍ ኤርፖርቱት

ዶጋሊ ኤርትራ ውስጥ የሚገኝ ቦታ ሲሆን፤ የደርግ መንግስት #የዶጋሊድልበዓል ሕዝባዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር እና ዶጋሊ ላይ የመታሰቢያ ሀውልት እንዲቆም አድርጎም ነበር፡፡ ጣሊያኖችም በጦርነቱ ለተሰዉ ወታደሮቻቸው ሮም ላይ የመታሰቢያ ኀውልት አቁመውላቸዋል፡፡

⏹ እስሌማን ዓባይ #የዓባይልጅ
#Yes_We_Blacks_Can

#አድዋ #Adwa #ዶጋሊ #አሉላአባነጋ #ኢትዮጵያ #Ethiopia #AdwaVictory #adwa127 #italy #VictoryOfDogali #AlulaAbanega #ድል #የአድዋድል #የዶጋሊድል #EslemanAbay #እስሌማንዓባይ #panafricanism