ጌታሁን ሄራሞ
ይህ በግለሰብ ደረጃ ራስን ከጥቃት መከላከል አለፍ ሲል ወደ ቡድናዊ መከላከልም ከፍ ሊል ይችላል። በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች ተሰራጭተው የሚኖሩ የብሔራቸው አባላት የሆኑ ዜጎች በሕይወት የመኖር መብታቸው በመንግስት ጥበቃ ካልተደረገላቸው ብሔር-ተኮር ቡድናዊ አደረጃጃትና ትጥቅ ሊጎለብት ይችላል..”Counter-resistance” እውን እየሆነ በሂደትም የሀገሪቱ ሰላም የሚናጋባቸው አጥቢያዎች እየሰፉ ሊመጡ ይችላሉ። ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ መንግስት ዜጎችን ከጥቃት ለመከላከል ባለመቻሉ የተፈጠሩ አንደንድ ቡድኖችን “ኢ-መደበኛ ታጣቂ” እያለ ቢከሳቸው ለመፈጠራቸው የራሱም አስተዋጽኦ እንዳለ መገንዘብ አለበት።