የኢትዮጵያ የዉጭ ግንኙነት

የኢትዮጵያ የዉጭ ግንኙነት

መንደርደሪያ

የኢትዮጵያ የዉጭ ግንኙነት ከክርስቶስ ልደት በፊት ከእየሩሳሌም ከህንድ ከቻይናና ከፋርስ (ወይም ከዛሬዋ ኢራን) ጋር ሲካሄድ የነበረ ነው። የኢትዮጵያን የቆየ ግንኙነት ለማየት ከ1521 አመቶች በፊት ነብዩ ሞሃምመድ ተከታዮቻቸው በችግር ላይ በነበሩበት ሰአት ወደ ኢትዮጵያ ሂዱ ማለታቸው ትልቅ ምስክር ነው። ከተራ ፖለቲካ ባለፈም ኢትዮጵያ የፍትህ ሃገር መሆኑዋን የመጀመሪያዎቹን የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ተቀብላ ህይማኖቱን ለማጥፋት ከተነሱ ሃይሎች ተከላክላ አድናለች።  ብዙዎች የማያዉቁትና በጣም አስደናቂው ግን በኢትዮጵያና በዘመኑ የሃያሎች ሁሉ ሃያል በነበረችው በፖርቱጋል መካከል የተመሰረተው የመጀመሪያው ግንኙነትና ከዚያም አልፎ በአለማችን የመጀመሪያ የጦር ትብብር ነው። ይህም ገና እንዳሁኑ አሜሪካ ገና ሳትመሰረትና አፍሪካዉያን በባሪያ አሳዳሪ ባእዳን አስተዳደር ዉስጥ ሳይገቡ በ16 ክፍለ ዘመን ነበር:: ይህ የመጀመሪያው በሁለት ክፍለ አለማት መካከል የተመሰረተው ግንኙነት እስከ የጦር ትብብር የደረሰና የሃያሉን የኦቶማንን የግዛትና የሃይማኖት መስፋፋት አላማን የሰበረ ነው።

ሌላው አስገራሚ ነገር ፖርቱጋሎች ይዘዉት የመጡት የዘመኑ የመጀመሪያው መተኮሻ መሳሪያ ወይም ጠብመንጃ/ራይፍል (Rifle) ጥቂት በመሆኑና ግማሹም ክርስቶፈር ዳጋማም የመጀመሪያዉን ዉጊያ ሲያደርግ በመዘረፉ ኢትዮጵያዉያንና ፖርቱጋሎች በመተባበር ጠብ መንጃን ኢትዮጵያ ዉስጥ መስራትና ማባዛታቸው ታዉቆአል። ለዚህም ይሆናል ኢትዮጵያዉያን የመሳሪያውን ስም ጠብ መንጃ (የተጣላን ሰው ማባረሪያ) ብለው ስም ያወጡለት። አንዳንድ ሰዎች ግን ባለማወቅም ይሁን በሌላ ምክንያት ስሙን ያወጡትለት ፖርቱጋሎች ናቸው በማለት ብዥታን ይፈጥራሉ። ያው እንደተለመደው ላሊበላን የሰሩት አሮፓዉያን ናቸው እንደሚሉት የተዛባ ታሪክ እንዳይሆን ታሪክን ከስሩ መቅዳት አለብን!

በሀገሮች መካከል የመጀመሪያው የዘመነ ግንኙነት የተፈጠረው 1799 ሲሆን ኢትዮጵያው አለክሳንደር ፑሽኪን ሞስኮው ዉስጥ የተወለደው እኤአ በ1798 ነው። በሩሲያና በኢትዮጵያ መካከል ደሞ ዘመናዊ ግንኙነት የተመሰረተ ነው በ18ኛው ክፍለዘመን ነው።ይህ የሚያስተምረን ታሪክ እራሱን ስለ ሚደግምና ዲፕሎማቶች ታሪክን ካላወቁ ከሌሎች ሃገሮች ጋር ጥሩ መወዳጀትን ለመፍጠር እንደሚቸገሩ ነው። ወደፊት በዚህ ሃሳብ እንደምናየው ኢትዮጵያ የብዙ ሃገሮችን ልብና አስተሳሰብ የሚማርኩ ቀደም ሲል የተሰሩ መሰረቶች አሉአት:: 

የኢትዮጵያና የእንግሊዝ መንግስት ግንኙነት በንግስት ቪክቶሪያና በአጼ ቴዎድሮስ ዘመንም የነበረ ቢሆንም በደንብ ቅርጽ ይዞ የተመሰረተው በአጼ ምኒልክ ዘመን ነው።  የአጼ ተዎድሮስ ልጅ (የልዑል አለማየሁ) ሃዉልትም ለማስታወሻ ያህል እዚሁ እንግሊዝ ሃገር ዉስጥ ይገኛል::

በ1902 አ/ም በራስ መኮንን ወልደሚካል የተመራው የመልእክተኞች ቡድን በለንደን

Ras Mekonnen and Ethiopian delegation in London in 1902
Ras Mekonnen (Father of Emperor Haile Selassie) and Emperor Edward the VII with other Ethiopian delegates in London (1902)

 

 

 

 

 

 

 

እንደ እኤአ በ1902 አጼ ምኒልክ በራስ መኮንን ወልደሚካኤል (የአጼ ሃይለስላሴ አባት) የሚመራ መልእክተኛ የኤድዋርድ ፯ኛውን ዘዉድ መድፋት ለመሳተፍ ለንደ መጥተው ነበር። ከራስ መኮንንጋር ፭ ከፍተኛ የኢትዮጵያ መልእክተኞች መጥተው ነበር::  እነሱም:-

ፊታዉራሪ ሃይለስላሴ ዓባይደር

ከንቲማ ገብረዎልድ ደስታ

መምህር ገብረ እግዚአብሄር

ፊታዉራሪ አባታቦርና

ሚካኤል ብሩ ናቸው።

ራስ መኮንን ለንደን እንደገቡ የኤድዋርድ ፯ኛዉን መታመምና በዚያም የተነሳ የዘዉድ መድፋቱ ስነስርአት መተላለፉን እንዳወቁ ወደ ዌስት ሚንስተር አቤይ (ገዳም) በመሄድ ለጤንነታቸው ጸልየዉ የወርቅ መስቀል ስጦታም አበርክተዉላቸዋል። ራስ መኮንንና መልእክተኞቹ የአጼ ተዎድሮስን ልጅ የልኡል ዓለማየሁን መቃብርም ከመጎብኘታቸውም በላይ  ከእንግሊዝ በተጨማሪ ፈረንሳይን ጀርመንን ጣሊያንን እና ቱርክን በመጎብኘት በኢትዮጵያና በነዚህ አገሮች መካከል ከፍተኛ መቀራረብን ፈጥረዋል። ንጉሰ ነገስት ኤድዋርድ ፯ኛ ከ፲፻፱፻፪ እስከ ፻፱፻፲ ድረስ የታላቁዋ ብሪታኒያና የህንድ ንጉስ ነበሩ።

ይህ የረጅም ዘመን ግንኙነት በአጼ ሃይለስላሴና በንግስት አልሳቤት ዘመን ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ንግስት ኤልሳቤት ኢትዮጵያን ሲጎበኙ ቀዳማዊ ሃይለ ስላሴም በይፋ እንግሊዝን ከመጎብኘታቸውም በላይ በፋሽት ኢጣሊያ ወረራ ጊዜ ንጉሰ ነገስቱ መኖሪያቸውን ለንደን በማድረግ በጄነቫና በሌሎች ሃገሮች በመዘዋረር በመጨረሻም ከእንግልዝ መንግስት ጋር ግምባር ፈጥረው የጣሊያን ጦር ከአፍሪካ ተጠራርጎ እንዲወጣ አድርገዋል። በፋሽት ወረራ ዘመን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን ተሰልፈው የፋሽስቶችን ግፍ ለአለም በማሳወቅ ሲልቪያ ፓንክህርስት ትልቅ ሚና ተጫዉተዋል። ልጃቸው ሪቻርድ ባንክረስትና ቤተሰባቸው በሙሉ የኢትዮጵያን እዉነተና ታሪክ ሳይዛባ ለዓለም በማሳዎቅም ጭምር ባለዉለታ ናቸው።

ይሁን እንጂ በደርግና በወያኔ ዘመን ይሕንን የቆየ ግንኙነት ከማጠንከር ይልቅ አንዳንድ እፍራሽ ድርጊቶች በሁለቱም ሃገሮች በኩል ታይተዋል። በተለይ ወያኔ በኢትዮጵያ ስም ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ግንኙነቱን በሁለቱ ህዝቦች መካከል ከማድረግ ይልቅ ነገድን የተከተለ አድርጎታል።

በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያ ዉስጥ የዘር ማጥፋት የፈጸመዉን መለስ ዜናዊዉን አግኖ ፋዉንዴሽን መንገዶችን እና ህንጻዎችን በስሙ ለመሰየም የተደረጉት ጥረቶች በለንደን ኢትዮጵያዉያን ሊከሽፍ ችሎአል። በቅርቡም ወያኔ የኢትዮጵያን መከላከያ ጦር ወሮ በመላው ኢትዮጵያ ላይ ክህደት ሲፈጽም አንዳንድ የእንግሊዝ የፓርላማ አባል ነን የሚሉ ሰዎች “ትግሬ ነጻ ከወጣች የእንግሊዝ መንግስት ይወቃት” የሚል እጅግ አደገኛና የሁለቱን ወዳጅ ሃገሮች ግንኙንት አደጋ ላይ የሚጥል ሕገወጥ የሆነ ፕሮፓጋንዳ በትዩተርና በሌሎች የህዝብ መህገኛኛ አዉታሮች ሲያስተጋቡ በለንደን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ግለሰቦች በሁለቱ አገሮች መካከል ለዥም ጊዜ የቆየው ግንኙነት በጥቂት ታሪክን በማያዉቁ ሰዎች እንዳይበላሽ ትግል አድርገው ይህንን አደገኛ ተንኮል አክሽፈዋል። ለዚህ ነው ታሪክን ማወቅ ለዉጭ ግንኙነት እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው የምንለው። እዚህ ላይ ማጤን ያለብን አምባሳደር ተብለው በየሃገሩ ከተቀመጡት ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች በላይ በውጭ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባሎች የሃገራቸውን ጥቅምና ደህንነት ለመጥበቅ በበጎ ፈቃዳቸው መስራት እንደሚችሉ ነው። አሁን ባለንበት የዉስጥ መረብ ዘመን የኢምባሴዎች አስፈላጊነትም እየደበዘዘ በመሄድ ላይ ነው። 

 

Ethiopia and Morocco
UNITED STATES – FEBRUARY 16: Morocco’s King Hassan and Emperor Haile Selassie of Ethopia meet in Carlyle Hotel, Manhattan. (Photo by Frank Hurley/NY Daily News Archive via Getty Images)
Ethiopia and China
HIM Haile Selassie and Chairman Mao Tsedung of China

ዲፕሎማስይ ምንድነው? 

ዲፕሎማስይ የሚለው ቃል ከግሪክ የተገኘ ነው። “ዲፕሎ” ማለት የታጠፈ የተደረበ ሲሆን “ማ” ደሞ ወረቀት ወይም ሌላ ነገር ሊሆን ይችላል። ዲፕሎማሲይ የመደራርደርና የአገሮችን ግንኙነት በሰላም ተግባብቶ የመጠበቅ የጥበብ ሙያ ነው።

26 July 1959 HIM Haile Selassie & President Admiral Americo Thomaz at Cais Lisbon, Portugal
26 July 1959 HIM Haile Selassie & President Admiral Americo Thomaz at Cais Lisbon, Portugal

የዲፕሎማሲይ ግንኙነት የተለያየ ትርጉም ወይም ፍቺ ቢኖረዉም ሁሉም የሚስማሙበት (The art of dealing with people in a sensitive and tactful way) ዲፕሎማሲይ በሰዎች መካከል ያሉ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋቸዉን ጉዳዮችን በጥበብ  መያዝ ነው። አንድ ዲፕሎማት በእዉቀት የላቀ ግርማ ሞገስ ያለውና ሃገር ወዳድ ከሆነ እራሱንም ሆነ የወከለዉን ህዝብ ያስከብራል::

የዲፕሎማስይ ጥቅም

የእንደራሴ ጽ/ቤትን (ኢምባሲይ) መክፈትና መልእክተኞችን (ዲፕሎማትን) የመሾም ዋናው አላማ ከሌሎች ሃገሮች ጋር ለመግባባት ለመወዳጀት ለመደራደር ዉሳኔዎችን ወደ ራስ ጥቅም ለማምጣት አጨቃጫቂ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ የሃይል እርምጃ ከመዉሰድ ለመቆጠብና ነገሮች በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኙ ለማድረግ ነው።

በሃገሮች መካከል ለሚደረጉ ግንኙነቶች ጠቃሚ የዲፕሎማስይ መመሪያዎች 

  • ብሄራዊ ጥቅምን ማስቀደም 
  • አሳማኝ መሆን 
  • ነገሮችን ገልጾ ማስረዳት መቻል 
  • ነገሮችን በስፋትና በጥልቀት ማየት 
  • ሌሎች የሚሉትን በጥንቃቄ ማዳመጥና መረዳት
  • ነቅቶ ነገሮችን ማስተዋልና መከታተል መቻል 
  • ችግሮችን በራስ ተማምኖና ጸንቶ መቁአቁዋም ናቸው።
Ethiopia and Iran
Ethiopia and Iran

እንዴት ነው ዲፕሎማሲይ የሃገርን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚረዳው?

ዲፕሎማስይ የሃገርን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲል ከዉይይት ዉጭ ሀይልና ሌሎች ቀዉስ የሚያስከትሉ አካሄዶችን አይመርጥም። ሆኖም ግን ማስፈራራትን ማስጠንቀቂያን መታቀብን በተቃዉሞ ስብሰባን እረግጦ መዉጣትን ከዚያም አልፎ በጦርነት ማስፈራራት ሊከሰቱ ይችላሉ:: በድርድር የማይመለስ የሃገርን ክብር አዋራጅ ወይም ድንበር ደፋሪና ህገ ወጥ የሆነ ነገር ገፍቶ ከመጣ ግን እራስን መከላከል ያስፈልጋል።

የዲፕሎማስይ አይነቶች ወይም ክፍሎች

Politics of pacification: (የሰላምና የመረጋጋት ፖለቲካ): የዚህ ዲፕሎማስይ ጽንሰ ሃሳብ የሰላም መንገድን መከተል ሲሆን በሃገሮች መካከል ያለ ቅራኔን ማርገብ ከጸብ ጫሪነት መራቅና በመነጋገር አንዳንድ ነገሮችን በመቀብልም ሆነ በመስጠት ከስምምነት ላይ ለመድረስ ነው።  

Ethiopia and Russia
HIM Haile Selassie with the then President of USSR, Nikita Sergeyevich Khrushchev

Gunboat diplomacy (ባለ ጠብመንጃ ጀልባ ዲፕሎማስይ) የዚህ ዲፕሎማስይ መሰረት ሃይልን ወይም ጥንካሬን በማሳየትና አስተሳሰብን በመቆጣጠር በዉጭ ግንኙነት ማሸነፍ ወይም ተገዥ ማድረግ ነው።

Dollar diplomacy:  የብር (የገንዘብ) ዲፕሎማስይ) በብድር መልክ ገንዘብም ሆነ ሌሎች ቁሳቆሶችን በመስጠት ወደ ተረጅነት (እርዳታ ባርነት) ማስገቢያ ጦርነት አልባ ስልት ነው።

Public diplomacy (የህዝብ ዲፕሎማሲይ):  ይህ አካሄድ ከተለመደው ባህላዊ የዲፕሎማሲ ይለያል። በዚህ መንገድ የአንደኛው ሃገር መንግስት የሌሎች ሃገር መንግስታትና ህዝቦችን በሃሳብ በማሳመን እና በማግባባት ለማቅረብ የሚደረግ ነው። በዚህ የግንኙነት መንገድ ዋናዉን ሚና የሚጫወተው ህዝቡ የውጭ ግንኙነት እዉቀት ካቸው ባለሙያዎችና ፖለቲከኞች ጋር በመተባበር ነው። ይህ አካሄድ የሚፈልጉትን ነገር ለማድረግ በቀጥታ ጉቦ ከመስጠት ከማስፈራራትና ህይልን ከመጠቀም ይልቅ አማላይ ስጦታዎችን በመለገስ ይሆናል። ተልእኮዉም የሚነደፈው ለረጅም ጊዜ አላማ መሳካት ሲሆን በሃገሮቹ ቁንቁዋ ሬዲዮን ጣቢያዎች ባህላዊ ኤግዚቢሽኖችን ጉዞዎችንና ትምህርት ቤቶችን በመጠቀም የሀገሩን ባህልን ጭምር በሌሎች ሃገር ህዝቦች ላይ በማስረጽ  ነው።

Mengistu and Castro
President Mengistu and and President Castro

People’s diplomacy (የሰዎች ዲፕሎማሲይ) ማለት ሰዎች በታሪክና በሂደት እየተገናኙ በመግባባት ግንኙነቶችን ሲያዳብሩ ነው።

Intermediary diplomacy: (አስታራቂ ዲፕሎማሲይ):  ይህ ዲፕሎማሲይ በሃገሮች መካከል ጭቅጭቅ ሲፈጠር ሶስተኛ ሃገር ገብቶ ተከታታይ ዉይይቶችን በማድረግ ችግሩ ወደ ግጭት እንዳያመራ መፍትሄ የሚሰጥ ነው።

Economic diplomacy (የምጣኔ ሃብት ዲፕሎማሲይ): የሚያተኩረው በኢኮኖሚ ላይ ሲሆን ይህም በሚገቡና በሚወጡ ሸቀጦች ላይ የዉጭ ሃገር ባለሃቶችን በመፍቀድና በአለም አቀፍ ግንኙነት ላይ ትብብርን የሚጠይቅ ነው። ይህ ዲፕሎማሲይ የአንድን ሃገር የምጣኔ ሃብት ጥቅም በአለም አቀፍ ደረጃ ለማረጋገጥ ይደራደራል።

Sylvia Pankrust Defender of Ethiopia

Digital (electronic) diplomacy: (የዉስጥ መረብ ዲፕሎማሲይ) ይህ አካሄድ መረጃንና የዘመናዊ መገኛ መንገዶችን በመጠቀም የግንኙነት መሰናክሎችን ማጽዳት ነው። በዚህ አሰራር ዉስጥ የዜና አዉታሮችን ማህበራዊ ገጾችን ድረ ገጾችንና ሌሎች አለም አቀፍ የመረጃ ምንጮችን በመጠቀም የዉጭ የጥቅም መመሪያን (ፖሊሲይን) እና የመረጃ ፕሮፓጋንዳን በዉስጥ መረብ ማሰራጨት ነው።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት ከሌሎች የዉጭ ሃገሮች ጋር ያላት ግንኙነት

ዲፕሎማሲይ በተለያዩ ሃገሮች መካከል በረጅም ጊዜ የሚገነባ ግንኙነት ነው። ኢትዮጵያን ከተለያዩ ሃገሮች ጋር የብዙ ዘመን ግንኙነት ቢኖራትም ይህንን እርሾ ዘው ወዳጅ ለማፍራት የሚጥሩ የተማሩና ሃገር ወዳ ኢትዮጵያዉያን ቦታቸውን እንዲይዙ ካላደረግን ብዙ ወዳጆቻችንን ማጣት ብቻ ሳይሆ ጠላት ልናደርጋቸው እንችላለን። ለምሳሌ በእንግሊዝ እና በኢትዮጵያ በአሜሪካና በኢትዮጵያ በሜክሲኮና በኢትዮጵያ በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል የነበረው ጥብቅ ግንኙነት ሙያ በሌላቸው መልእክተኞችና በጸረ ኢትዮጵያ ተሹአሚዎች እየተበላሸ ሃገራችንን አሁን አለችበት ደረጃ ላይ አድርሶአታል። 

Historian Professor Richard Pankhrust friend of Ethiopia
Historian Professor Richard Pankhrust

 ታሪክ እራሱን ይደግማል

ከ1936-1938 (ኤአ) ሜክሲኮ ቻይና ኒውዜላንድ ሶቬት ህብረት ስፓኝና አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ፋሽት ጣሊያን ያደረገችዉን ወረራ ተቃውመው ነበር። ሆኖም ግን እስከመጨረሻ ከኢትዮጵያ ጋር የቆሙት ሩሲያ ሜክሲኮ ነውዜላንድና ቻይና ነበሩ። ሩሲያ በአድዋዉም ጦርነት ጊዜ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ቆማ የማይናወጥ ወዳጅነቱዋን አሳይታለች:: ታሪክ እራሱን ይደግማል ማለት ይሄ ነው። ምንም እንኩዋን የእንግሊዝ መንግስት ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ከኢትዮጵያ ጎን ባይቆምም ብዙዎች ሊያኮስሱት የሚሞክሩት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የሙሶሎኒን ፋሽት ጦር ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ከመላው አፍሪካ ተጠርጎ እንዲወጣ የረዳው በንጉስ ሃይለስላሴና በእግሊዝ መካከል የተደረገው የጋራ የጦር ትብብር ነው። አሁን በአይናችን በምናይበትና በጆሮአችን በምንሰማበት በዚህ አስቸጋሪ የአሸባሪው ወያኔ ዘመን ሩሲያ ሜክሲኮና ቻይና እንደገና ከኢትዮጵያ ጎን መቆማቸዉን እና የማይታጠፍ ወዳጅነታቸውን ማሳየታቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ ከፍተኛ ግምት ሊሰጠው የሚገባ የክፉ ቀን ዉለታ ነው።

ማጠቃለያ

የአለም አቀፍ ሁኔታ ከፍተኛ የለዉጥ እመርታ እያሳየ ስለሆነ ዘመኑን የሚመጥን ሁሉን አሳታፊና ሁሉን አቀፍ የሆነ የዲፕሎማሲይ እና የአለም አቀፍ ስርአት የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነን። ሃያላን ሃገሮች ሌሎች በአለም ያሉ ሃገሮችን በሙሉ አሳትፈው በአለም አቅፍ ግንኙነት ላይ ብቻ ሳይሆን በአለም አቀፍ ህግና ስርአት ላይ ክለሳ አድርገው እንደአግባቡ ግንኙነቶችን ካላስተካከሉ ወደፊት ችግር ሊፈጠር እንድሚችል ለመገመት አያስቸግርም። 

Ethiopia and Yugoslavia
Nov. 11, 1963 – Tito Welcomes Haile Selassie: Emperor Haile Selassie of Ethiopia has arrived in Yugoslavia on a visit at which he will exchange views …

የዘመኑ ፈጣን የዉስጥ መረብ የመርጃ መለዋውጭያ መንገድ የዲፕሎማሲን አሰራር በጥልቀት ሊቀይረው እንድሚችል ለመረዳት የመረጃ መሰብሰቡን ስራ ሰውሰራሽ እዉቀት (Artificial Intelligence) እንዴት እየተካው እንደሄደ ማየቱ በቂ ነው። ይህም ማለት በአሁኑ ሰአት ብዙ ሺህ ዶላር እየተከፈላቸው በመላው ሃገር ከተላኩ ዋጋቢስ የጎሳ አቀንቃኝ መልእክተኞች ይልቅ የተማሩ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዉን በግልም ሆነ በቡድን ማህበራዊ መገናኛዎችን ድረገጾችን እና ሌሎች መንገዶችን በመጠቀም በአለም አቀፍ ደረጃ እንዴት ኢትዮጵያን ከወያኔና ከነሱ ተከታይ ከሆነው ሃገር አፍራሽ ኦነግ አንደተከላከሉና አመርቂ ዉጤት አንዳመጡ መገንዘቡ ብልህነት ነው::

Share:

Share on facebook
Share on twitter
Share on linkedin
Share on pinterest

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

On Key

Related Posts

VK Russian online social media and social networking service

© 2022 Esleman Abay. All rights reserved.

Follow Us

Categories