Notice: Function _load_textdomain_just_in_time was called incorrectly. Translation loading for the matomo domain was triggered too early. This is usually an indicator for some code in the plugin or theme running too early. Translations should be loaded at the init action or later. Please see Debugging in WordPress for more information. (This message was added in version 6.7.0.) in /home/eslemanabaycom/public_html/wp-includes/functions.php on line 6131
በመቀሌ የህወሃት ጨካኝ ውሳኔ - የዓባይ ፡ ልጅ
Deprecated: Creation of dynamic property OMAPI_Elementor_Widget::$base is deprecated in /home/eslemanabaycom/public_html/wp-content/plugins/optinmonster/OMAPI/Elementor/Widget.php on line 41

በመቀሌ የህወሃት ጨካኝ ውሳኔ

መከላከያ ሰራዊቱ መቀሌ ከተማን በቅርብ ርቀት ከበባ ማስገባቱን ተከትሎ የህወሓት ቡድን “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” በሆነ ውሳኔ እየፈፀመው ያለው ተግባር አሳዛኝ ነው።
የሽብር ቡድኑ በመቀሌ ከተማ እስር ላይ የነበሩ በርካታ ታራሚዎችን በመበተን በዘራፊነት አሰማርቶ ወደ በረሃ በመሸሽ ላይ መሆኑ ነው የተሰማው።

ህወሃት ይህን መሰል ድርጊት ሲፈፅም የመጀሪያው አይደለም። 2013 ዓ/ም ላይ መከላከያ ሰራዊቱ መቀሌን ከበባ ውስጥ ሲያስገባ በተመሳሳይ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን በመልቀቅ በከተማው ስርዓት አልበኝነት እንዲሰፍን፣ የህዝቡ ቀሪ ንብረት እንዲዘረፍና በርካቶች በማጅራት መቺ ህይወታቸውን እንዲያጡ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
ይህ ህወሃታዊ ሴራ መከላከያ ሰራዊቱ ከተማ በማረጋጋት ስራ እንዲጠመድ ያለመ ሲሆን፣ ቡድኑ ለህዝብ ደንታ እንደሌለው በድጋሚ ያረጋገጠ ድርጊት ነው።

ይሁንና የመቀሌ ህዝብ የህወሃትን ሴራ በተደጋጋሚ በመመልከቱ ራሱን የማትረፍ አማራጮችን እየወሰደ ነው ተብሏል። መደበቂያ ያለው የከተማዋ ነዋሪ የሌባ ሲሳይ ላለመሆን የቻለውን ንብረት ይዞ ወደ ገጠር አካባቢዎች በመሸሽ ላይ እንደሆነ ነው የተሰማው።
#ENDF

Share:

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

VK Russian online social media and social networking service
Categories