Notice: Function _load_textdomain_just_in_time was called incorrectly. Translation loading for the matomo domain was triggered too early. This is usually an indicator for some code in the plugin or theme running too early. Translations should be loaded at the init action or later. Please see Debugging in WordPress for more information. (This message was added in version 6.7.0.) in /home/eslemanabaycom/public_html/wp-includes/functions.php on line 6131
“እርዳታችሁን እዛው ያዙ!” - የዓባይ ፡ ልጅ
Deprecated: Creation of dynamic property OMAPI_Elementor_Widget::$base is deprecated in /home/eslemanabaycom/public_html/wp-content/plugins/optinmonster/OMAPI/Elementor/Widget.php on line 41

“እርዳታችሁን እዛው ያዙ!”

ማሊ በፈረንሳይ የሚደገፉ NGOs ከሀገሪቱ እንዲወጡ አዘዘች

ማሊ ከሩሲያ ጋር ያላትን ትብብር ተከትሎ ፈረንሳይ ለሀገሪቱ የምትሰጠውን ድጋፍ ለማቆም የወሰነችው በቅርቡ ነበር። ይህን ተከትሎ የማሊ መንግሥትም የፈረንሳይን ውሳኔ የተቀበለ ሲሆን፣ በምላሹም በፈረንሳይ ያንግስት ፈንድ የሚደረጉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች NGOs ከማሊ ለቀው እንዲወጡ ውሳኔ አሳልፏል።

የማሊ መንግስት በዛሬው ዕለተ ሰኞ አመሻሽ ላይ እንዳስታወቀው ሰብአዊ በተባሉ መስኮች የሚንቀሳቀሱትን NGOs ጨምሮ በፈረንሳይ ፋይናንስ የሚደረጉ ወይም ድጋፍ የሚያገኙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን(መያድ) እንደሚያግድ ይፋ አድርጓል።
በርካታ መያዶች በማሊ የጤና፣ የምግብ እንዲሁም በትምህርት መስኮች ተሰማርተው የሚገኙ ሲሆን ባማኮ ያሳለፈችውን ውሳኔ ተከትሎ እንደ CCFD፣ Terre-Solidaire፣ Handicap International፣ Médecins du Monde፣ እና Oxfam ጨምሮ የተለያዩ NGOs የፈረንሳይ ዕርዳታ ማቋረጥን ተከትሎ የሚወሰዱ ርምጃዎች የሚመለከታቸው ይሆናል።
የፈረንሳዩ የዜና አውታር France 24 ጉዳዩን ሲዘግብ የማሊ መንግስትን “ጁንታው አመራር” በሚል ርዕሰ አንቀፅ ሲገልፅ ተስተውሏል።

#የዓባይልጅ

france #France24 #bamako

Share:

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

VK Russian online social media and social networking service
Categories