
ሶስቱ አሉታዎች: አል-ፋሻቃ ~ አል-ቡርሃን ~ አል-ሲሲ እና የኢትዮጵያ ጥንቃቄ
“ጦር ሜዳውን ራስህ ካልመረጥክ አትዋጋ።” ይለናል የጥንታዊው ቻይናዊ sun Tzu የጦርነት ጥበብ አንደኛው መርሆ..። ምክንያቱን ሲያብራም “..ጠላት በመረጠው ጦር ሜዳ መዋጋትህ አንተ ከምታውቀውና ከተዘጋጀህበት በተለዬ ጠላትህ በላጭ ይሆናልና..” ሲል ይመክራል። ነገረ-አልፋሻቃን የተመለከቱ መረጃዎች መውጣት መጀመራቸውም ከመሰል ስትራቴጂዎች አንፃር መመርመር ተገቢ ስለመሰለኝ ነው ይህን ፅሁፍ ያዘጋጀሁት..።
እንደ መረጃዎቹ “..በአልፋሻቃ መሬቶች የነበሩ (አልቡርሃን-መራሽ) የሱዳን ወታደሮች ከቦታው ለቅቀው እየወጡ ናቸው..” በማለት የተሰራጩ ሲሆን፤ የመረጃው አቅጣጫም ሆነ አመጣጡ ግን ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግ መሆኑ ነው የሚያመዝነው..።









